አንጋፋው የአርባምንጭ መካነ ኢየሱስ ቴክኒክ ኮሌጅ ለአርባምንጭ ጨርቃጨርቅ እንዲሁም ለብሔራዊ ቡድን የተጫወቱ ተጫዋቾችን ያፈራ ተቋም ነው።
Posted inArticles
እግር ኳስ
Posted by
admin
No Comments
የአርባምንጭ መካነ ኢየሱስ ቴክኒክ ኮሌጅ በ1964 ዓ.ም የተመሠረተ አንጋፋ ተቋም ነው። ኮሌጁ ሲመሠረት በእንጨትና በብረታ-ብረት ሥራ ጐበዝ ተማሪዎችን ከ6ኛ ክፍል ተቀብሎ ሥልጠና መስጠት ጀመረ።ከ1973 እስከ 1976 በእንጨት ሥራ፣ በብረታ-ብረት ሥራና በአውቶ ሜካኒክስ ከ10ኛ ክፍል ተማሪዎችን ተቀብሎ በ10+2 ማሠልጠኑን ቀጠለ። ከ1977 ዓ.ም ጀምሮ ደረጃውን ወደ 10+3 በማሳደግ ተማሪዎችን በዲፕሎማ ደረጃ ማስመረቊን ቀጠለ። ኮሌጁ እንደገና በአዲስ መልክ በመደራጀት ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ ዛሬ የሚጠራበትን ‘የአርባምንጭ መካነ ኢየሱስ ቴክኒክ ኮሌጅ’ ስም በመያዝ ከደረጃ 1 እስከ ደረጃ 4 ድረስ ብቊ ተማሪዎች እያፈራ ዛሬ ላይ ደርሷል። ኮሌጁ ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ በአራት የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራሞች የዕውቅና ፈቃድ አግኝቶ ማስተማር ላይ ይገኛል።
Post navigation
Previous Post
ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ
Next Post
Sunshine የእግር ኳስ ማሠልጠኛ ተቋም